በቦሌ ክ/ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ዋና ዋና አገልግሎቶች

1. በአካባቢ ብክለት እና ተጽእኖ ግምገማ ቡድን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
  • ስለአካባቢ ብክለት፣ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት
  • ብክለት በሚያደርሱ ተቋማት ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ ፣
  • የብክለት መጠን በመለካት እርምጃ መውሰድ ፣
  • የፕሮጀክቶችን የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነዶችን በመገምገምና መቆጣጠር የማስተካከያ ሀሳብ መስጠት
  • የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ እና የአካባቢ ተፅእኖ ክዋኔ ሪፖርት መከታተል
2. በአየር ንብረት ለውጥ ቡድን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
  • ስለአየር ንብረት ለውጥ፣ ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት፣
  • ለአየር ንብረት ለውጥን በዘርፍ መ/ቤቶች በዕቅድ መካተቱን ማረጋገጥ ፣
  • ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ተጋላጭ የህበረተስብ ክፍሎች ድጋፍና ክትትል ፣
  • የኢነርጂ ቴክኖሎጂዎችን የዲዛይንና የፕሮሞሽን ስራ በመስራት ለተጠቃሚዎች ማስፋፋት፥
3. በየተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ቡድን አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • ስለህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት፣
  • በጥናትና ምርምር የተመሰረተ የብዝሃ ህይወትና ሥርዓተ ምህዳር ቁጥጥርና ክትትል ማድረግ፣
  • በብዝሃ ሕይወትና ሥርዓተ ምህዳር ዙሪያ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠት፣
  • የአረንጓዴ ቦታዎች ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውን መከታተልና መቆጣጠር፣
  • የደን ሃብት ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንዲሰጥ ማድረግ ፣

4. በ ማዕድን ሀብት ፈቃድና አስተዳደር ቡድን የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • ስለማዕድን ሀብት ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት፣
  • ለአዲስ እና ነባር የኮንስትራክሽን ማዕድን ፈቃድ አስተያየት መስጠት ፣
  • ነጭ ድንጋይ ማምረት ፈቃድ ፣ የወንዝ ዳር አሸዋ ማውጣት ፈቃድ ፣
  • በማዕከልና በክ/ከተማ የተሰጡ ፈቃዶችን ማስተዳደር/መከታተል፣ መቆጣጠርና መረጃ ማደራጀት
  1. ገጽ-1
  2. ገጽ-2